


የአማራ ክልል ዉኃ አገልግሎቶች ማህበር በከተማችን ከሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎች ጋር በጋራ በመሆን የዉኃ ማጣሪያ ተጠቃሚ ደንበኞች ብዛትን ለማወቅ ቤት ለቤት እየዞሩ መረጃ የመሰብሰብና ደንበኞችን በቤት ዉስጥ የዉኃ ንፅህና አጠባበቅና አያያዝ ችግር ምክንያት ዉኃ ሊበከል ስለሚችል ማጣሪያ ገዝተዉ እንዲጠቀሙ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ይህን ተከትሎ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ በአንዳንድ የከተማችን ነዋሪዎች ዘንድ ዉኃ ተበክሏል ተብሎ ሀሰተኛ መረጃ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን መረጃዉ የተሳሳተና ከእዉነት የራቀ መሆኑን እናሳስባለን፡፡